የኢትዮጵያ ህዝብ የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ካንገሸገሸው ሰንብቷል። ለዚህም የ1997 ብሄራዊ ምርጫ ውጤት በቂ
ምስክር ነው።ድምጹን ተነጥቆ ከያኔ ጀምሮ አፉ ተለጉሞና ነጻነቱን አጥቶ ሲኖር ከርሞ ዛሬ ግን ከምንጊዜውም ይበልጥ
ከሰሜን አስከ ደቡብ፤ ከምስራቅ እስክ ምዕራብ፤መሃልን ጨምሮ ራሱ የህወሃት/ኢህአዴግ የጻፈውን “ህገ-መንግስት”
መሰረት በማድርግ የመብት ጥያቄዎችን እያነሳ በሰላማዊ መንገድ የአሻፈረኝነትንና የበቃኝን ጩሀቱን እያሰማ ነው።
ለዚህ ሰላማዊ ለሆነው የህብረተሰቡ የመብት ጥያቄ ግን ትክክለኛና አግባብ ያለው መልስ እንደመስጠት ፈንታ
አንባገነናዊው የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት የሃይል እርምጃ በመውሰድ የንጹሃን ዜጎችን ደም እያፈሰሰ ነው።read more