Monday, March 5, 2012
የምንፈልገውን ለውጥ ለማምጣት (ባሕር ከማል)
“ለውጥ “ የሚባለውን ቃል ስንሰማ ወዲያውኑ በአዕምሮአችን ውስጥ የሚቀረፀው ጥሩነቱ ብቻ ነው። መጥፎ ውጤት የሚያስከትል ለውጥ መኖሩን ባንዘነጋም እምብዛም ትኩረታችንን አይስብም። የለውጥ ውጤት መቶ በመቶ ጥሩ ይሆናል ብሎ መገመት ባይቻልም በምኞት ደረጃ ግን ሁሉም የሚመኘው ጥሩውን ነው። አንዳንዴ ግን ምናባቱ ከዚህ የባሰ አይመጣም ይባላል።ይህ ከጭንቀትና ነባሩን ሁኔታ ለመቋቋም በማይቻልበት ደረጃ ላይ ሲደረስ ከብሶት የሚመነጭ እንጂ ምን ጊዜም የባሰ ሊመጣ እንደሚችል ቀደም ብሎ መገመቱ አይከፋም። ለጥሩ ውጤት ይበልጥ እንድንዘጋጅ ያደርገናልና።